X
የደብራችን የኮተቤ መካነ ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና ቤተ-ክርስቲያን ወልድ ዋሕድ ሰ/ት/ቤት ከደብሩ ከተመሠረተበት ሐምሌ 22 ቀን 1,976 ከወራት በፊት ለደብሩ የሰ/ት/ቤት አገልግሎት እና የደብሩ ምሥረታ ክብረ በዓል አከባበር መንፈሳዊ ዓላማ ባነገቡ ጥቂት ወጣቶች እና አገልጋይ ካህናት ፣ ዲያቆናት አማካኝነት በ1,976 ግንቦት ወር ተመሠረተ።

Contact Info

  • አድራሻ
  • info@weldwahed.org
  • Contact Us: 0915573949
    0911473190

Blog Details

Weld Wahed > ዜና > Uncategorized > የወልድ ዋሕድ  ሰ/ት/ቤት የርቀት ትምህርት  ተማሪዎች  ትምህርታዊ የጉዞ መርሐ ግብር ተካሔደ ።

የወልድ ዋሕድ  ሰ/ት/ቤት የርቀት ትምህርት  ተማሪዎች  ትምህርታዊ የጉዞ መርሐ ግብር ተካሔደ ።

ሐምሌ 27 2017 ዓ.ም – ወልድ ዋሕድ ሚዲያ

በኮተቤ መካነ ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና ቤተክርስቲያን የወልድ ዋሕድ ሰ/ት/ቤት የርቀት  ክፍል አዘጋጅነት  ከአዲስ አበባ በ50 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ወደ ሚገኘው ገዋሳ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስና አቡነ ሀብተማርያም ቤተክርስትያን ልዩ የአንድነት ጉዞ መርሐ ግብር  ሐምሌ 27/2017 ዓ.ም ተካሒዷል ።

በዕለቱም  የተለያዩ መርሐ ግብራት የቀረቡ ሲሆን  የዋሻ ጉብኝት፣   መርሐ-ግብራችን ተጀመረ የመክፈቻ ዝማሬ በሕብረት ከዘመርን በኋላ የሕብረት ማዕድ ተጋራን በማስከተልም ቃለ እግዚአብሔር በ ዲ/ን እስጢፋኖስ ደሳለኝ ተሰጥቷል በመቀጠልም ዘማሪ መብዓ ጽዮን ዝማሬ ከቀረበ በኋላ የጥያቄዎቻችሁ መልሶች በሚል መርሐ ግብር በመጋቢ ሐዲስ ሐብተማርያም ምላሽ እና ማብራሪያ ተሰጥቷል በመጨረሻ በመልዓከ ፀሐይ ቆሞስ አባ ገብረማርያም በጸሎት ተጠናቋል ።

በዚህ መንፈሳዊ ጉዞ ላይ 400 የርቀት ተማሪዎች ተሳትፈዋል።

በነገሮች ሁሉ የረዳን አምላከ ቅዱሳን ይክበር ይመስገን

Leave A Comment

All fields marked with an asterisk (*) are required